ኤይድስ (acquired immunodeficiency syndrome) ለሚለው ምህፃረ-ቃል ነው።ሲንድሮም የሚለው ቃል አንድን አይነት ህመም ወይ ሥቃይ የሚያመለክቱ በዛ ያሉ ምልክቶች ማለት ነው።ኤይድስ በዛ ያሉ በሽታዎችን ሊያመለክት የሚችል ሃሳብ ሆኖ፣ ሁሉም ግን በኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ከመያዝ የተነሳ መተፈጠረ የተፈጥሮ የመከላከል ሃይል መዳከም ሳቢያ የሚከሰቱ ናቸው።
የምርመራ ውጤት ኤይድስ ነው የሚባለው ምን ሲያሳይ ነው?
የምርመራ ውጤትን ኤይድስ ነው ለማለት የሚደረጉ መስፈርቶች ካገር አገር ይለያያሉ። ሁንኛ መለያው የኣጋጣሚ-ጠባቂ በሽታዎች በተደጋጋሚና ባስጊ ሁኔታ መከሰት ነው።ከኤች.አይ.ቪ ተሸካሚነት ወደ የኤይድስ ህመምተኛነት የሚደረገው ሽግግር ከጊዜ ጋር የሚያድግ ነው። ባብዛኛው ግን ያንድ ኣሳሳቢ ወይም የብዙ ትናንሽ በሽታዎች መከሰት ኤይድስ መከሰቱን ያሳያሉ።